ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናል
Posted onሰው በሰው ፊት ሲቆም ጻድቅ ሆኖ መታየት ይችላል፡፡ ጻድቃን የተባሉት ግን ራሳቸውን በጌታ ፊት ሲያዩ ድካማቸውና ስንፍናቸው ግልጽ ሆኖ ይታያቸዋል፡፡ መጀመሪያ ከራሱ አንጻር አይቶ ማጥመቁን እምቢ ያለው ዮሃንስ በኃላ ግን የኢየሱስ የጽድቅ ማንገሥ ዓላማን በማየት ታዘዘውና አጠመቀው፡፡
ሰው በሰው ፊት ሲቆም ጻድቅ ሆኖ መታየት ይችላል፡፡ ጻድቃን የተባሉት ግን ራሳቸውን በጌታ ፊት ሲያዩ ድካማቸውና ስንፍናቸው ግልጽ ሆኖ ይታያቸዋል፡፡ መጀመሪያ ከራሱ አንጻር አይቶ ማጥመቁን እምቢ ያለው ዮሃንስ በኃላ ግን የኢየሱስ የጽድቅ ማንገሥ ዓላማን በማየት ታዘዘውና አጠመቀው፡፡
But one thing is assured, God is looking after the one He has sent. Heaven is ready to guide and provide.Don’t be afraid of the disturbed evil forces, Heaven is with you and for you! Just remember God with us, Emmanuel!
ማሪያም ሊትወልድ ያለውን ልጅ በሌላ ዮሴፍ በፈለገው ስም መጥራት አይችልም ማለት ነው፡፡ ምናልባት እግዚአብሄር ጣልቃ ገብቶ ለዮሴፍ ይህንን ሃላፊነት ባይሰጠው፣ ኢየሱስ ምን ተብሎ ይጠራ ኖሮአል? በሀገራችን በስም አሠጣጥ ባህል ምናልባት “የሴት ልጅ፣ አፍራሽ፣ ድንጋታ፣ አሳምኖት፣ አስጨናቂ፣ ወይም ሌሎችም በዚህ ላይ ከመናገር የተቆጠብኳቸው ሥሞች ሊሰጡት ይችሉ ነበረ፡፡ እነዚህ ስሞች ደግሞ ከዓላማው ጋር የማይሄዱ ናቸው፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር፣ “ለጻድቁ” ዮሴፍ የራዕይ አግባብነት ያለውን ስም ለልጁ እንዲያወጣለት ተናገረው፡፡ “ኢየሱስ” ወይም “አዳኝ” “ፈይሳ” ተብሎ እንዲጠራ፡፡ በመገለጡ መሠረት፣ ይህ ስም “ሥጋ ለሆነው ቃል” የተሰጠው፣ እርሱ “ሕዝቡን ሁሉ ከኃጢአታቸው ስለሚያድናቸው” ነው፡፡
የዮሃንስ አገልግሎት የእግዚአብሄርን መንግሥት መቅረቧን ሃጢአተኞች ለሆኑት ለሰዎች ልጆች በሙሉ መናገር ነበረ፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ለሰዎች ሁሉ መናገር ዋጋ ያስከፍላል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ለእውነተኛ አገልጋይ (ቢሮው ምንም ይሁን ምን) መሠረቱ፣ መለኪያውና መመዘኛው እንዲሁም መመሪያው ነው፡፡
እጅግ አስደናቂ የሆነ የምህረት እጅ ዛሬ ለሚመለሱ ሁሉ ተዘርግቶ አለ፡፡ “ኑ!” እያሌ ይጣራል፡፡ “ኑ!”
ቀጣዩ ዘመን እንደዛሬው ሁሉም ተቀላቅሎ የሚኖርበት፣ ስንዴና ገለባ ተሰባጥሮ የሚቀመጥበት ጊዜ አይደለም፡፡ የሚወሰደው እርምጃም እንደዛሬው የማባበልና የርህራዬ አይደለም፡፡ ጎተራውም እሳቱም ሁለተኛ ስንዴውና ገለባው ላይቀላቀሉ ለመለዬት የተዘጋጁ ቦታዎች ናቸው፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሆኖ፣ ስለሰቃዮቹ ይጨነቅ ነበረ፡፡ እግዚአብሄር ይቅር ካላላቸው፣ እያደረጉት ያሉ ነገር ወደ ዘላለም ቅጣት ይወስዳቸዋል፡፡ “ክፉውን መልካም መልካሙን ክፉ ለሚሉ፥ ጨለማውን ብርሃን ብርሃኑንም ጨለማ ለሚያደርጉ፥ ጣፋጩን መራራ መራራውንም ጣፋጭ ለሚያደርጉ ወዮላቸው!” ይላልና እግዚአብሄር (ኢሳ 5፡20-24)፡፡ ወገኖቼ፣ በበሽታ፣ በችግር፣ በረሃብ፣ በጦሪነት፣ በእርጅና፣ በተለያዩ አደጋዎች ይህችን ዓለም ከመልቀቃችን በፊት ምን ያክል ጊዜ እንደቀረን አናውቅም፡፡ ግን ይህችን የቀረችንን እድሜ እንዴት እናሳልፍ? እግዚአብሄርን በመሳደብ ወይስ ለምህረት ወደ ተዘረጋችው የእግዚአብሄር እጅ በመሸሽ?
እግዚአብሄር ያልሰጠንን ጽድቅ ለራሳችን ብንቆጥር ራስን መሸንገል እንጂ ድነት አናገኝበትም፡፡ በሕይወት የሚያኖረው እግዚአብሄር ራሱ በዕቅር ባይነቱ የሚሠጠው ጽድቅ ነው፡፡
ይህንን ምሳሌ ኢየሱስ ሲናገር አድማጮች ሰምተው የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንዲቀበሉ ነው፡፡ ሰሚዎቹ ኢየሱስ ከጎናቸው ሆኖ እየለመናቸው ያለጽድቅና ምህረት እንዳይመለሱ ነው፡፡ ሰሚዎቹ የራሳቸውን ጽድቅ ትተው የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንዲቀበሉ ነው፡፡ የምህረትንና የጉብኝታቸውንም ጊዜ እንዳይንቁ ነው፡፡ ኢየሱስን ለማየትና ለመስማት መምጣታቸው ካልቀረ፣ ለምንድር ነው ከነ ኃጢአት መኖር? ኢየሱስ በእግዚአብሄር ፊት ራሱን ስላዋረደው ሰውዬ ሲናገር “ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ” አለ፡፡
ሰውዬው እየዞረ አሥርቱን ከተማ በጌታ ምህረትና ድርግት ሞላው፡፡ እርሱ ስለስነ-መለኮት መናገር አይችልም፡፡ ስለኢየሱስ ማንነትም በዘመኑ ሰዎች ዘንድ ያለውን ኮንትሮቬርሲ መመለስ አይችልም፡፡ ግን ያየውንና የተደረገለትን መሰከረ፡፡ በእግዚአብሄር ጣት የተሠራውም ሥራ ሕያው ስለነበረ፣ ሰዎች ይሰሙት ጀመር፡፡
ለተደረገልን ማንኛውም ነገር እግዚአብሄርን ማመስገን ስንለማመድ፣ ብዙ ተጨማሪ በረከቶችን ከእግዚአብሄር እንቀበላለን፡፡ ስለመቀበሉ ብቻም አይደለም፡፡ እስቲ አስቡ፣ ሕዶ በጌታ ፊት ተገኝቶ ከእርሱ ጋር መነጋገርስ ምነኛ ትልቅ በረከት ነው፡፡ ወደ እርሱ ቀርቦ ከሥጋ ፈውሱ የሚበልጠው ምህረቱና ደንነቱ በሕይወታችን መኖሩን ከአፉ ስንሰማ አያስደስትምን?
ኢየሱስ ደቄ መዛሙርቱ ስለተረጉ ነገሮች መደሰታቸውን አይቶ፣ በሃላ ደግሞ ወደ ችግር እንዳይገቡ የዘላቂ ደስታቸው አቅጣጫና ምንጭ ምን መሆን እንዳለበት አሳያቸው፡፡ ደስታቸው መናፊስት ስለተገዙላቸው ወይም ስለታዘዙአቸው ብቻ ከሆነ፣ አንድ ቀን መናፊስት ከመታዘዝ እምቢ የሚልበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል (ጾምና ጸሎትም ካልተጨመረ የሚያስቸግርበት ጊዜ አለና)፡፡ ሰዎችም ስብከታቸውን ከመቀበል ይልቅ ሊያሳድዱአቸው የሚነሱበት ጊዜም ሩቅ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን ስማቸው በሰማይ ተጽፎላቸዋልና ዘላለማቸው ዋስትና አለው