Sermons

ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናል

Posted on

ሰው በሰው ፊት ሲቆም ጻድቅ ሆኖ መታየት ይችላል፡፡ ጻድቃን የተባሉት ግን ራሳቸውን በጌታ ፊት ሲያዩ ድካማቸውና ስንፍናቸው ግልጽ ሆኖ ይታያቸዋል፡፡ መጀመሪያ ከራሱ አንጻር አይቶ ማጥመቁን እምቢ ያለው ዮሃንስ በኃላ ግን የኢየሱስ የጽድቅ ማንገሥ ዓላማን በማየት ታዘዘውና አጠመቀው፡፡

Events

Merry Christmas

Posted on

But one thing is assured, God is looking after the one He has sent. Heaven is ready to guide and provide.Don’t be afraid of the disturbed evil forces, Heaven is with you and for you! Just remember God with us, Emmanuel!

Sermons

Kalu Yadinal

Posted on

ማሪያም ሊትወልድ ያለውን ልጅ በሌላ ዮሴፍ በፈለገው ስም መጥራት አይችልም ማለት ነው፡፡ ምናልባት እግዚአብሄር ጣልቃ ገብቶ ለዮሴፍ ይህንን ሃላፊነት ባይሰጠው፣ ኢየሱስ ምን ተብሎ ይጠራ ኖሮአል? በሀገራችን በስም አሠጣጥ ባህል ምናልባት “የሴት ልጅ፣ አፍራሽ፣ ድንጋታ፣ አሳምኖት፣ አስጨናቂ፣ ወይም ሌሎችም በዚህ ላይ ከመናገር የተቆጠብኳቸው ሥሞች ሊሰጡት ይችሉ ነበረ፡፡ እነዚህ ስሞች ደግሞ ከዓላማው ጋር የማይሄዱ ናቸው፡፡
ስለዚህ እግዚአብሄር፣ “ለጻድቁ” ዮሴፍ የራዕይ አግባብነት ያለውን ስም ለልጁ እንዲያወጣለት ተናገረው፡፡ “ኢየሱስ” ወይም “አዳኝ” “ፈይሳ” ተብሎ እንዲጠራ፡፡ በመገለጡ መሠረት፣ ይህ ስም “ሥጋ ለሆነው ቃል” የተሰጠው፣ እርሱ “ሕዝቡን ሁሉ ከኃጢአታቸው ስለሚያድናቸው” ነው፡፡

Sermons

min litayu

Posted on

የዮሃንስ አገልግሎት የእግዚአብሄርን መንግሥት መቅረቧን ሃጢአተኞች ለሆኑት ለሰዎች ልጆች በሙሉ መናገር ነበረ፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ለሰዎች ሁሉ መናገር ዋጋ ያስከፍላል፡፡ የእግዚአብሄር ቃል ለእውነተኛ አገልጋይ (ቢሮው ምንም ይሁን ምን) መሠረቱ፣ መለኪያውና መመዘኛው እንዲሁም መመሪያው ነው፡፡

Sermons

prepare the way

Posted on

እጅግ አስደናቂ የሆነ የምህረት እጅ ዛሬ ለሚመለሱ ሁሉ ተዘርግቶ አለ፡፡ “ኑ!” እያሌ ይጣራል፡፡ “ኑ!”
ቀጣዩ ዘመን እንደዛሬው ሁሉም ተቀላቅሎ የሚኖርበት፣ ስንዴና ገለባ ተሰባጥሮ የሚቀመጥበት ጊዜ አይደለም፡፡ የሚወሰደው እርምጃም እንደዛሬው የማባበልና የርህራዬ አይደለም፡፡ ጎተራውም እሳቱም ሁለተኛ ስንዴውና ገለባው ላይቀላቀሉ ለመለዬት የተዘጋጁ ቦታዎች ናቸው፡፡

Sermons

Go home justified

Posted on

እግዚአብሄር ያልሰጠንን ጽድቅ ለራሳችን ብንቆጥር ራስን መሸንገል እንጂ ድነት አናገኝበትም፡፡ በሕይወት የሚያኖረው እግዚአብሄር ራሱ በዕቅር ባይነቱ የሚሠጠው ጽድቅ ነው፡፡
ይህንን ምሳሌ ኢየሱስ ሲናገር አድማጮች ሰምተው የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንዲቀበሉ ነው፡፡ ሰሚዎቹ ኢየሱስ ከጎናቸው ሆኖ እየለመናቸው ያለጽድቅና ምህረት እንዳይመለሱ ነው፡፡ ሰሚዎቹ የራሳቸውን ጽድቅ ትተው የእግዚአብሄርን ጽድቅ እንዲቀበሉ ነው፡፡ የምህረትንና የጉብኝታቸውንም ጊዜ እንዳይንቁ ነው፡፡ ኢየሱስን ለማየትና ለመስማት መምጣታቸው ካልቀረ፣ ለምንድር ነው ከነ ኃጢአት መኖር? ኢየሱስ በእግዚአብሄር ፊት ራሱን ስላዋረደው ሰውዬ ሲናገር “ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ” አለ፡፡

Sermons

Tell Your Story

Posted on

ሰውዬው እየዞረ አሥርቱን ከተማ በጌታ ምህረትና ድርግት ሞላው፡፡ እርሱ ስለስነ-መለኮት መናገር አይችልም፡፡ ስለኢየሱስ ማንነትም በዘመኑ ሰዎች ዘንድ ያለውን ኮንትሮቬርሲ መመለስ አይችልም፡፡ ግን ያየውንና የተደረገለትን መሰከረ፡፡ በእግዚአብሄር ጣት የተሠራውም ሥራ ሕያው ስለነበረ፣ ሰዎች ይሰሙት ጀመር፡፡

Sermons

ሊያከብሩ የተመለሱ

Posted on

ለተደረገልን ማንኛውም ነገር እግዚአብሄርን ማመስገን ስንለማመድ፣ ብዙ ተጨማሪ በረከቶችን ከእግዚአብሄር እንቀበላለን፡፡ ስለመቀበሉ ብቻም አይደለም፡፡ እስቲ አስቡ፣ ሕዶ በጌታ ፊት ተገኝቶ ከእርሱ ጋር መነጋገርስ ምነኛ ትልቅ በረከት ነው፡፡ ወደ እርሱ ቀርቦ ከሥጋ ፈውሱ የሚበልጠው ምህረቱና ደንነቱ በሕይወታችን መኖሩን ከአፉ ስንሰማ አያስደስትምን?

Sermons

መሸከም አትችሉም

Posted on
ቢነገራቸው መሸከም እንደማይችሉ ኢየሱስ ያውቅ ነበረ፡፡ye cannot bear them now. “12 የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። 13 ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። 14 እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና። 15 ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ፦ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ።”ዮሓ 16፡12-15

ደቄ መዛሙርቱ ሊመጣ ስላለው ነገር ቢነገራቸው መሸከም እንደማይችሉ ኢየሱስ ያውቅ ነበረ፡፡ ስለዚህ “የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም” አላቸው፡፡ መንፈስ ቅዱ ሲመጣ የሚናገር ብዙ አለና፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት መቀበልና እርሱን መስማት የኢየሱስን ፈቃድ ማድረግ ነው፡፡ አንዳንዶቹን የሕይወትና የአገልግሎታችንን ሁኔታዎች፣ ጉዞውን ከመጀመራችን በፊት አውቀናቸው ቢሆን በራሳችን እንደማናልፋቸው ስለምናውቅ ጉዞውን ሁሉ የምንጀመር አይመስለኝ፡፡ የመሸከም አቅማችንን የሚያውቅ ጌታ ዛሬም ከአቅማችን በላይ አይሠጠንም፡፡ ስለዚህ ለዛሬና ለሚመጣው ማንኛውም ሁኔታ፣ መንፈስ ቅዱስን መጠበቅ፣ እርሱን መታመንና ቃሉን መስማት እጅግ የበጀናል፡፡

Uncategorized

መልካም ግንኙነት

Posted on
መልካም ግንኙነት ,wilesofthedevil, Mekane Yesus in Scotland, salvation, prayer, resist,

“እግዚአብሄር አምላኬ ሆይ፣ ስለምትወደኝ እጅግ አድርጌ አመሰግንሃለሁ፡፡ ክቡር በሆነውን መልከህና ምሳሌህ ስለፈጠርከኝ ተመስገን፡፡ ነገር ግን ብዙ ጊዜ ተመላልሰህ በጠበቅህኝ ቦታ ስላላገኘህኝ ዕቅርታ እጠይቅሃለሁ፡፡ ከውድቀተ አንስቶኝ፣ ከጥፋቴም መልሶኝ ሕይወትን ይሰጠኝ ዘንድ ስለእኔ ስለሞቴውና ከሞትም ስለተነሳው ልጅህ ኢየሱስ ክርስቶስ አከብርሃለሁ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከወደደኝና ስለእኔ ነፍሱን ከሰጠው ከልጅህ ከኢየሱስ ጋር መኖርን እፈልጋለሁ፡፡ በምህረትህ ተቀበለኝ፡፡ ያወቅሁ እየመሰለኝ ተታልዬ ከገባሁበት ማንኛውም ሁኔታ አንቴ አውጣኝ፡፡ ስሜን በሕይወት መዝገብ ጻፍልኝ፡፡ አንቴ የምትወደው ዓይነት ሰውም ሆኜ ከአንቴ ጋር በመልካም ግንኙነት መኖር እንዲችል በጸጋህ እርዳኝ፡፡ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፡፡ አሜን፡፡”