Sermons

እግዚአብሄርን ማስገረም

Posted on
እግዚአብሄርን ማስገረም አይቻልም፡፡ መካነ ኢየሱስ, መካነ የሱስ በስኮትላንድ, እጅህ ንጹህ አይደለም, No surprise!, ስብከት በተክሉ , የግላስጎ አመኞች, የእግዚአብሄርን ጸጋ አልጥልም, እሬ እኔ ማን ነኝ, ያንስብሃል ምስጋናዬ ያንስብሃል ጌታ, ምህረት የበዛለት , Amazing grace, saved by grace, Mekane Yesus, ECMYIS, Mekana Yasus in Scotland, Glasgow christians, Evangelical chuch in glasgow, wash your hand, hand washing

ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት (በመገኘቱ ውስጥ) ተቀመጠ። በዚያም ሆኖ ትክክለኛ ማንነቱን እና የእግዚአብሔርን ቸርነት ማሰብ ጀመሬ። እግዚአብሔር ልብን እንደሚያውቅም ተረዳ።

ሞት ተፈርዶበት እያሌ ከዚያ አስመልጦት በህይወት ያኖረውን ጌታ ንጉሥ ሆኖ ማገልገል ላይ የሚገኘው ዳዊት እግዚአብሄርን ባለእዳ ማድረግ ይችላል ወይ? እኛስ ብንሆን፣ እግዚአብሄር ሳያደርግልን፣ ለእግዚአብሄር የምናቀርበው ነገር ምን ይኖረናል?

Sermons

Easter about Future

Posted on

ከኢየሱስ ከሞት ከመነሳት እውነት (ሃቅ) በተስተጀርባ በተለይ ዛሬ ላይ ያለን ትውልድ በትክክል ማሰብና መገንዘብ ያለብን እውነት እንዳለ አምናለሁ፡፡ እርሱም ትንሳኤው ኢየሱስ ተመልሶ እንደሚመጣ እርግጠኞች ያደርገናል፡፡

ጌታ ኢየሱስ ገና ከመገደሉ በፊት ለተከታዮቹ ደጋግሞ ኣሳልፎ ሊሠጥና መከራ ሊቀበል እንዳለ፣ ሊሰቀልና በሶስተኛው ቀን ከሞት ስለመነሳቱ እና ወደ አባቱ እንደሚሄድ ተናግሮ ነበረ፡፡ እያንዳንዱም ነገር ከሦስት ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ተፈጸመ፡፡ ኢየሱስ እንደ ተናገረ ሆኖአል፡፡
(Sermon By Teklu, ECMYIS, Scotland, UK)

Sermons

ክርስቲና ስለ ሕይወት ነው

Posted on
ecmyis sunday service, Mekane Yesus in Scotland, Christianity, Glasgow church,

ዓለማዊ ዜጎችን በወንጌሉ ቃል የሰማያዊ ዜጎች የማድረግ ሥራ ውስጥ የመንፈሳዊው ድንበር ጥሰት መዘዞች አሉበት፡፡ ይህ ደግሞ መገለጫው በቤተሰዎች መካከል፣ በዘመዶች መካከል፣ በወዳጆች መካከል፣ በህብረተሰብ መካከል የሚመጡ አለመግባባቶች፣ አለመስማማቶችና በተለይም ስለቃሉ በሚነሱት ስዴቶች ናቸው፡፡ ክርስቲና ለሕወትና ለጥሪ የሚንኖርበት ሕይወት እንጂ የምቾት ሕይወት ብቻ አይደለም፡፡ ያ ማለት ደግሞ ክርስቲያኖች ፈጽሞ የምቾት ሕይወት አያስፈልጋቸውም፣ ወይም በምቾት መኖር አይችሉም ማለት አይደለም፡፡ የእግዚአብሄር ደስታ፣ ሠላም፣ በረከት፣ አብሮነትና መንፈስ የደስታቸውና የምቾታቸው መሠረት ነውና፡፡… የሚላኩ ሰዎች ወይም ደቀ መዛሙርት በተለያዬ መንገድ የሚደግፉአቸውን ከእነርሱ በታች አድርገው መቁጠር አይገባቸውም፡፡ በእግዚአብሄር ፊት ሁለቱም እኩል ዋጋ አላቸውና፡፡

Teachings

እምነታችን

Posted on

እንኳን ወደ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ በስኮትላንድ ድረ-ገጽ በደህና መጡ፡፡ የቤተክርስቲያናችን ስም ምንጫችን ከሆነችው እናት ቤተክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ በቀጥታ የመጣ ሆኖ በስኮትላንድ አውድና ኗሪዎችን ማዕከል ባደረገ መልኩ የተመሠረተች ቤተክርስቲያን ናት፡፡ የቤተክርስቲያንቱ ልዩ መታወቂያ የሆነው መካነ የሱስ ትርጉሙ የኢየሱስ መኖሪያ ሥፍራ ማለት ነው፡፡ በአጭሩ ለመጥራት እንዲመች “ መካነ የሱስ በስኮትላነድ ” የምለውን […]