Sermons

እልካችኋለሁ

Posted on
እልካችኋለሁ ፡፡

“ሂዱ፤ እነሆ፥ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ፡፡” በተኵላ መካከል ማርኮ ለመመለስ ተልእኮ ወስዶ የምንቀሳቀስ በግ ተመልከቱ፡፡ ለራሱም ተስፋ የሌለው ይመስላል፡፡ የወንጌልን ሰባኪነት ተልዕኮ ይዞ የምንቀሳቀስ ሰው እንዲሁ ነው፡፡ ተግዳሮቱ ብዙና ከባድ ነው፡፡ግን የተልዕኮው ባለበት እግዚአብሄር ደግሞ የበለጠ ብርቱና ታማኝ ነው፡፡ ስለዚህ ስመችም ሳይመችም መልእክቱ መተላለፍ አለበት፡፡ “የእግዚአብሔር መንግሥት ግን ወደ እናንተ እንደ ቀረበች ይህን እወቁ”

Sermons

መሸከም አትችሉም

Posted on
ቢነገራቸው መሸከም እንደማይችሉ ኢየሱስ ያውቅ ነበረ፡፡ye cannot bear them now. “12 የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም። 13 ግን እርሱ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ ወደ እውነት ሁሉ ይመራችኋል፤ የሚሰማውን ሁሉ ይናገራል እንጂ ከራሱ አይነግርምና፤ የሚመጣውንም ይነግራችኋል። 14 እርሱ ያከብረኛል፥ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋልና። 15 ለአብ ያለው ሁሉ የእኔ ነው፤ ስለዚህ፦ ለእኔ ካለኝ ወስዶ ይነግራችኋል አልሁ።”ዮሓ 16፡12-15

ደቄ መዛሙርቱ ሊመጣ ስላለው ነገር ቢነገራቸው መሸከም እንደማይችሉ ኢየሱስ ያውቅ ነበረ፡፡ ስለዚህ “የምነግራችሁ ገና ብዙ አለኝ፥ ነገር ግን አሁን ልትሸከሙት አትችሉም” አላቸው፡፡ መንፈስ ቅዱ ሲመጣ የሚናገር ብዙ አለና፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ምሪት መቀበልና እርሱን መስማት የኢየሱስን ፈቃድ ማድረግ ነው፡፡ አንዳንዶቹን የሕይወትና የአገልግሎታችንን ሁኔታዎች፣ ጉዞውን ከመጀመራችን በፊት አውቀናቸው ቢሆን በራሳችን እንደማናልፋቸው ስለምናውቅ ጉዞውን ሁሉ የምንጀመር አይመስለኝ፡፡ የመሸከም አቅማችንን የሚያውቅ ጌታ ዛሬም ከአቅማችን በላይ አይሠጠንም፡፡ ስለዚህ ለዛሬና ለሚመጣው ማንኛውም ሁኔታ፣ መንፈስ ቅዱስን መጠበቅ፣ እርሱን መታመንና ቃሉን መስማት እጅግ የበጀናል፡፡

Sermons

መዳን በኢየሱስ

Posted on
መዳን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ ነው፡፡

በምዋርተኝነት መንፈስ የተያዘችና በጥንቆላዋ (በምዋርቷ) ለጌቶቿ ብዙ ትርፍ ታስገኝ የነበረች ሴት ናት፡፡ እርሷ ከሚትናገረው ትንቢት (ምዋርት) ይልቅ እነጳውሎስ የሚሰብኩት ስብከት ለመዳን ጠቃሚ እንደሆነ ትናገራለች፡፡ እነርሱም የሚላኩለት ጌታ እርሷ ከሚታገለግላቸው ጌቶችና ከምዋሪት መንፈስ የሚሻል እንደሆነም ጠቁማለች፡፡ “የመዳንን መንገድ የሚነግሩአችሁ እነዚህ ሰዎች የልዑል አምላክ ባሪያዎች ናቸው” እያለች፡፡

Events

ትንሳኤ

Posted on
እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡

እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡

ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡

ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡ (ቀጥሎ ለማንበብ ከላይ ያለውን ምስል ወይም ሪዕሱን ይጫኑ)

መልካም የትንሳኤ በዓል፡፡

Sermons

ለድሆች ወንጌል

Posted on
“ለድሆች ወንጌልን እሰብክ” ድህነት የገንዘብ እጦት ችግር ብቻ እንዳይደል ከዚህ እንገነዘባለን፡፡ ለደሃ ትልቁ የሚያስፈልገው ደግሞ ወንጌል ነው፡፡ ከወንጌል ሰው ሕይወትን ይጠግባል፣ ሠላምን ይጠግባል፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ ፍቅርን፣ ተስፋን፣ ወዘተ. ይጠግባል፡፡ECMYIS, mekane Yesus Scotland, Mekane Yesus in SCotland, Glasgow Mekane Yesus, Makane yesus is Glasgow, Mekana Yasuus, Lutheran Church Glasgow, Amharic Service, Oromo, Tigrigna, Christian church in Glasgow, Evangelical Christian church, Salvation,Ethiopinan church glasgow, Erthrian and Ethiopian Christian Church, sermons, Sunday service, Jesus Christ saves. he came to Nazareth, where he had been brought up: and, as his custom was, he went into the synagogue on the sabbath day, and stood up for to read.18 The Spirit of the Lord is upon me, because he hath anointed me to preach the gospel to the poor; he hath sent me to heal the brokenhearted, to preach deliverance to the captives, and recovering of sight to the blind, to set at liberty them that are bruised,19 To preach the acceptable year of the Lord.

“ለድሆች ወንጌልን እሰብክ” ድህነት የገንዘብ እጦት ችግር ብቻ እንዳይደል ከዚህ እንገነዘባለን፡፡ ለደሃ ትልቁ የሚያስፈልገው ደግሞ ወንጌል ነው፡፡ ከወንጌል ሰው ሕይወትን ይጠግባል፣ ሠላምን ይጠግባል፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ ፍቅርን፣ ተስፋን፣ ወዘተ. ይጠግባል፡፡ ሰላም ና መልካም እየመሰላቸው ወደ ሲሆል ከሚሄዱ ሰዎች የበለጠ ዕውር የለም፡፡ እግዚአብሄር የለም እያሉ ሰማይንና ምድርን የሞላውን እግዚብሄርን በመካድ ሕይወት ውስጥ ከሚኖሩ የበለጠ እውር ማን ነው? እግዚአብሄርን አገለግላለው፣ አመልካለሁ እያለ ግን በሠይጣን አገዛዝ ሥር ከሚኖር የበለጠ እውር ማን ነው? በአጠቃላይ የሕይወት መንገድ በአጠገቡ እያለ፣ በሞት ጎዳና ከሚራመድ ሰው የበለጠ እውር ማን ነው? ኢየሱስ የመጣው ለእነዚህ ሁሉ ነው፡፡

Sermons

ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ

Posted on
I will make you to become fishers of men አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ ወደማንችለው አገልግሎት እንደመጣን ይሰማን ይሆን? መዛሙርቱ ሰዎችን አጥማጆች ለመሆን የሚበቁ አልነበሩም፡፡ ኢየሱስ ግን "እንዲትሆኑ አደርጋችሃለሁ" አላቸው፡፡ ይህ ኢየሱስ ያለው ቃል ደግሞ ከንቱ ቃል አንዳልነበረ የደቀ መዛሙርት ሕይወትና የእኛ ራሳችን ክርስቲያኖች መሆን ይመሰክራል፡፡

ወደማንችለው አገልግሎት እንደመጣን ይሰማን ይሆን? እንዴትስ ይከናወንልናል እንል ይሆን? ደቀ መዛሙርቱ ሰዎችን አጥማጆች ለመሆን የሚበቁ አልነበሩም፡፡ በራሳቸው ሊሆኑም አይችሉም፡፡ ኢየሱስ ግን “እንድትሆኑ አደርጋችሃለሁ” አላቸው፡፡ ኢየሱስ ራሱ “እንድትሆኑ አደርጋችሃለሁ ” ብሎኣል፡፡ ይህ ኢየሱስ “እንድትሆኑ አደርጋችሃለሁ” ያለው ቃል ደግሞ ከንቱ ቃል አንዳልነበረ የደቀ መዛሙርት ሕይወትና የእኛ ራሳችን ክርስቲያኖች መሆን ይመሰክራል፡፡ ያ የኢየሱስ ቃል እውነትና ሕያው ሲለሆነ ነው እነስምዖን ጴጥሮስ በሺዎች ለሚቆጠሩት መመስከር የቻሉት፡፡

Teachings

እምነታችን

Posted on

እንኳን ወደ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ በስኮትላንድ ድረ-ገጽ በደህና መጡ፡፡ የቤተክርስቲያናችን ስም ምንጫችን ከሆነችው እናት ቤተክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ የሱስ በቀጥታ የመጣ ሆኖ በስኮትላንድ አውድና ኗሪዎችን ማዕከል ባደረገ መልኩ የተመሠረተች ቤተክርስቲያን ናት፡፡ የቤተክርስቲያንቱ ልዩ መታወቂያ የሆነው መካነ የሱስ ትርጉሙ የኢየሱስ መኖሪያ ሥፍራ ማለት ነው፡፡ በአጭሩ ለመጥራት እንዲመች “ መካነ የሱስ በስኮትላነድ ” የምለውን […]