Sermons

እግዚአብሄርን ማስገረም

Posted on
እግዚአብሄርን ማስገረም አይቻልም፡፡ መካነ ኢየሱስ, መካነ የሱስ በስኮትላንድ, እጅህ ንጹህ አይደለም, No surprise!, ስብከት በተክሉ , የግላስጎ አመኞች, የእግዚአብሄርን ጸጋ አልጥልም, እሬ እኔ ማን ነኝ, ያንስብሃል ምስጋናዬ ያንስብሃል ጌታ, ምህረት የበዛለት , Amazing grace, saved by grace, Mekane Yesus, ECMYIS, Mekana Yasus in Scotland, Glasgow christians, Evangelical chuch in glasgow, wash your hand, hand washing

ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት (በመገኘቱ ውስጥ) ተቀመጠ። በዚያም ሆኖ ትክክለኛ ማንነቱን እና የእግዚአብሔርን ቸርነት ማሰብ ጀመሬ። እግዚአብሔር ልብን እንደሚያውቅም ተረዳ።

ሞት ተፈርዶበት እያሌ ከዚያ አስመልጦት በህይወት ያኖረውን ጌታ ንጉሥ ሆኖ ማገልገል ላይ የሚገኘው ዳዊት እግዚአብሄርን ባለእዳ ማድረግ ይችላል ወይ? እኛስ ብንሆን፣ እግዚአብሄር ሳያደርግልን፣ ለእግዚአብሄር የምናቀርበው ነገር ምን ይኖረናል?

Events

ትንሳኤ

Posted on
እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡

እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡

ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡

ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡ (ቀጥሎ ለማንበብ ከላይ ያለውን ምስል ወይም ሪዕሱን ይጫኑ)

መልካም የትንሳኤ በዓል፡፡

Sermons

ኢየሱስ ሥራውን ቀጠለ

Posted on
I must work the works of him that sent me, while it is day: the night cometh, when no man can work. “ ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች ”Evangelical Church Mekane Yesus in Scotland, ECMYIS, Glasgow, Uk. Amharic service

ጌታ እየሱስ ብዙ የሚሠራቸው ሥራዎች ነበሩት፡፡ በተለይ ደግሞ አጋንንትን ማውጣት እና በሽተኞችን መፈወስ (ቁ.32)፡፡ ይህ ማለት የታሰሩንና ጤናቸውን ያጡትን የሰዎችን ልጆች ነጻ ማውጣት በቀረችው ጊዜ መፈጸም የሚፈልጋቸው ሥራዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ይህንን ዓላማውን ትቶ እንዲሄድና ከሄሮድስ የመግደል ዕቅድ እንዲያመልጥ ስመክሩት እንመለከታለን፡፡“ከፈሪሳውያን አንዳንዱ ቀርበው፦ ሄሮድስ ሊገድልህ ይወዳልና ከዚህ ውጣና ሂድ አሉት።” (ቁ 31)
ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ የነበረውን ተልዕኮ (ሚሽን) ጨርሶ ከመሄዱ በፊት የተወሰነ ወይም ጥቂት ጊዜ እንደነበረው ያውቅ ነበረ፣ ይናገርም ነበረ፡፡ “ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች” (ዮሓ 9፡4) ብሎአልና። ኢየሱስ ሰው ሊሠራበት የማይችልበት “ሌሊት” ይመጣል ሲል ሰው ሌሊቱ ሳይመጣ የተሠጠውን የቤት ሥራ በርትቶ መጨረስ እንዳለበት ለማሳሰብም ነው፡፡ …..

Sermons

ከጸጋው ቃል የተነሣ

Posted on
ሁሉም ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ከጸጋው ቃል የተነሣ እየተደነቁ፦ ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። ሉቃ 4፡22 “And all bare him witness, and wondered at the gracious words which proceeded out of his mouth. And they said, Is not this Joseph's son?” Luk 4:22 Glasgow city, Mekane Yesus congrigation, Scottish Ethiopians church, EECMY, ECMYIS, Mekane Yesus in Scotland, Mekane Yasus, Ethiopian Church in Glasgow, Scotland, Ethiopian Christina Community, Evangelical Church, Lutheran chuch in Glasgow, Scotland. we meet in St George's Tron Church, Church of Scotland, city center. Christian family, infant baptism is also practiced here. Eritrean Christian church from Lutheran chuch of Eritrea.

ኢየሱስ ያነበበው ክፍል እና የሚናገረው ነገር ወደ ማንነቱ ዕውቀት የሚመራ ቢሆንም፣ ሰዎች በእርሱ ማመን አልፈለጉም፡፡ በዓለማችን ውስጥ የሚፈጠሩት ሕብረተሰባዊ ቀውሶችም ሆነ መነቃቃቶች በአብዛኛቸው ቢጠኑ፣ ከተጽኖ አምጪ ንግግሮች ጋር ተያያዥነት እንዳላቸው እገምታለሁ፡፡ “የጠቢባን ቃል እንደ በሬ መውጊያ ነው” ፡፡ የበሬ መውጊያ የሚባለው፣ ደንባራውንና ደካማውን በሬ፣ ወደ ፊት ዘሎ እንዲሄድ የሚያደርገው ነው፣ ተኝቶም ከሆነ፣ ከተኛበት ቀስቅሶ የሚያስሮጥ ነገር ነው፡፡

Sermons

ለድሆች ወንጌል

Posted on
“ለድሆች ወንጌልን እሰብክ” ድህነት የገንዘብ እጦት ችግር ብቻ እንዳይደል ከዚህ እንገነዘባለን፡፡ ለደሃ ትልቁ የሚያስፈልገው ደግሞ ወንጌል ነው፡፡ ከወንጌል ሰው ሕይወትን ይጠግባል፣ ሠላምን ይጠግባል፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ ፍቅርን፣ ተስፋን፣ ወዘተ. ይጠግባል፡፡ECMYIS, mekane Yesus Scotland, Mekane Yesus in SCotland, Glasgow Mekane Yesus, Makane yesus is Glasgow, Mekana Yasuus, Lutheran Church Glasgow, Amharic Service, Oromo, Tigrigna, Christian church in Glasgow, Evangelical Christian church, Salvation,Ethiopinan church glasgow, Erthrian and Ethiopian Christian Church, sermons, Sunday service, Jesus Christ saves. he came to Nazareth, where he had been brought up: and, as his custom was, he went into the synagogue on the sabbath day, and stood up for to read.18 The Spirit of the Lord is upon me, because he hath anointed me to preach the gospel to the poor; he hath sent me to heal the brokenhearted, to preach deliverance to the captives, and recovering of sight to the blind, to set at liberty them that are bruised,19 To preach the acceptable year of the Lord.

“ለድሆች ወንጌልን እሰብክ” ድህነት የገንዘብ እጦት ችግር ብቻ እንዳይደል ከዚህ እንገነዘባለን፡፡ ለደሃ ትልቁ የሚያስፈልገው ደግሞ ወንጌል ነው፡፡ ከወንጌል ሰው ሕይወትን ይጠግባል፣ ሠላምን ይጠግባል፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ ፍቅርን፣ ተስፋን፣ ወዘተ. ይጠግባል፡፡ ሰላም ና መልካም እየመሰላቸው ወደ ሲሆል ከሚሄዱ ሰዎች የበለጠ ዕውር የለም፡፡ እግዚአብሄር የለም እያሉ ሰማይንና ምድርን የሞላውን እግዚብሄርን በመካድ ሕይወት ውስጥ ከሚኖሩ የበለጠ እውር ማን ነው? እግዚአብሄርን አገለግላለው፣ አመልካለሁ እያለ ግን በሠይጣን አገዛዝ ሥር ከሚኖር የበለጠ እውር ማን ነው? በአጠቃላይ የሕይወት መንገድ በአጠገቡ እያለ፣ በሞት ጎዳና ከሚራመድ ሰው የበለጠ እውር ማን ነው? ኢየሱስ የመጣው ለእነዚህ ሁሉ ነው፡፡

qophii

ልባችሁ እንዳይከብድ ተጠንቀቁ

Posted on
ልባችሁ እንዳይከብድ ያ ቀንም በድንገት እንዳይመጣባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፡፡ መካነ የሱስ፣ ግላስጎ መካነ የሱስ፣ ስኮትላንድ፣ ዪናይትድ ኪንግደም፣ Lutheran Church in Glasgow, ECMYIS, evangelical Church mekane Yesus in Scotland, Luk 21 25-36 'And there shall be signs in the sun, and in the moon, and in the stars; and upon the earth distress of nations, with perplexity; the sea and the waves roaring; Men's hearts failing them for fear, and for looking after those things which are coming on the earth: for the powers of heaven shall be shaken.

ሰው በእግዚአብሄር መታመን ሲያቅተው ነገሮችን ሁሉ በራሱ መጀመሪና መጨረስ ስለሚሞክር፣ በራሱ ዓቅም ልሠሩ ወደማይችሉ ነገሮች ስደርስ በብዙ ጭንቀርትና አላስፈላጊ የሕይወት ጎዞዎች ወስጥ ይገባል፡፡
ይህ ደግሞ በኢየሱስ ትምህርት ውስጥ እንደተገለጠው፣ የእግዚአብሄርን ቃል እንዳያፈራ በማድረግ ሰው ገለባ የሆነ ሕይወት ብቻ እንዲኖር ያደርጋል፡፡ በማቴ13፡22 “በእሾህ መካከል የተዘራውም ይህ ቃሉን የሚሰማ ነው፥ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት መታለል ቃሉን ያንቃል፥ የማያፈራም ይሆናል።” ስለዚህ ጌታ ኢየሱስ በዚህ ዓይነት ሕይወት ውስጥ እያላችሁ “ያ ቀንም በድንገት እንዳይመጣባችሁ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ” ብሎ አስጠነቀቀ፡፡ ሐዋሪያውም ጳውሎስ፣ “ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።” (ፊልጵ 4፡6)