ለድሆች ወንጌል
Posted on“ለድሆች ወንጌልን እሰብክ” ድህነት የገንዘብ እጦት ችግር ብቻ እንዳይደል ከዚህ እንገነዘባለን፡፡ ለደሃ ትልቁ የሚያስፈልገው ደግሞ ወንጌል ነው፡፡ ከወንጌል ሰው ሕይወትን ይጠግባል፣ ሠላምን ይጠግባል፣ እረፍትን፣ ደስታን፣ ፍቅርን፣ ተስፋን፣ ወዘተ. ይጠግባል፡፡ ሰላም ና መልካም እየመሰላቸው ወደ ሲሆል ከሚሄዱ ሰዎች የበለጠ ዕውር የለም፡፡ እግዚአብሄር የለም እያሉ ሰማይንና ምድርን የሞላውን እግዚብሄርን በመካድ ሕይወት ውስጥ ከሚኖሩ የበለጠ እውር ማን ነው? እግዚአብሄርን አገለግላለው፣ አመልካለሁ እያለ ግን በሠይጣን አገዛዝ ሥር ከሚኖር የበለጠ እውር ማን ነው? በአጠቃላይ የሕይወት መንገድ በአጠገቡ እያለ፣ በሞት ጎዳና ከሚራመድ ሰው የበለጠ እውር ማን ነው? ኢየሱስ የመጣው ለእነዚህ ሁሉ ነው፡፡