Events

ትንሳኤ

Posted on
እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡

እንኳን ለጌታችን ኢየሱስ ትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ፡፡ ህንን ቀን ስናስታውስና ስናከብር ትልቁ ቁምነገር እግዚአብሄር ለእኛ በግል ስላደረገልን ነገር ማወቅና ማመስገን ስንችል ነው፡፡ ምክንያቱም ጌታ ኢየሱስ ጎልጎታ በሚባል ኮረብታ ላይ በመስቀል ላይ የሞተው እኛን ፍለጋ መጥቶ ነው፡፡ ለመሞትም የፈቀደው እኔና እናንተ እንዳንሞት ስለፈለገ ነው፡፡ ይህንን በዓል ሲናከብር የበዓሉን ዋና የሆነውን ኢየሱስንና ዋጋው የተከፈለላትን ነፍሳችንን ረስተን በተለያዩ ነገሮች መባከን የለብንም፡፡

ኢየሱስ ዛሬ ሙት አይደለም፡፡ ኢየሱስ ተነስቶአል፡፡ ኢየሱስ ሁለተኛም ሊሞት አይችልም፡፡ ኢየሱስ “… አትፍራ፤ ፊተኛውና መጨረሻው ሕያውም እኔ ነኝ፥ ሞቼም ነበርሁ እነሆም፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ሕያው ነኝ፥ የሞትና የሲኦልም መክፈቻ አለኝ” ብሎአል፡፡(ራእ 1፡17-18)፡፡

ጌታ ኢየሱስ ከትንሳኤው ቦኃላ ከተከታዮቹ ከጠየቃቸው ነገሮች የተወሰኑትን ማየት የራሳችንን የትንሳኤው አከባበር ሥርዓታችንን ለመፈተሸ ይረዳናል ብዬ አምናለሁ፡፡ (ቀጥሎ ለማንበብ ከላይ ያለውን ምስል ወይም ሪዕሱን ይጫኑ)

መልካም የትንሳኤ በዓል፡፡

Sermons

ነውር

Posted on
ኢያሱ 5፡9-12 9 እግዚአብሔርም ኢያሱን፦ ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ አለው፤ ስለዚህ የዚያ ስፍራ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ጌልገላ ተብሎ ተጠራ። 10 የእስራኤልም ልጆች በጌልገላ ሰፈሩ፤ ከወሩም በአሥራ አራተኛው ቀን በመሸ ጊዜ በኢያሪኮ ሜዳ ፋሲካ አደረጉ። 11 ከፋሲካውም በኋላ በነጋው የምድሪቱን ፍሬ የቂጣ እንጎቻ ቆሎም በዚያው ቀን በሉ። 12 በነጋውም ከምድሪቱ ፍሬ ከበሉ በኋላ መናው ቀረ፤ ከዚያም በኋላ ለእስራኤል ልጆች መና አልመጣላቸውም፤ ነገር ግን በዚያው ዓመት የከነዓንን ምድር ፍሬ በሉ።

በምድረበዳ ውስጥ መና ማግኘት ትልቅ በረከት ነው፡፡ መልካም በሆነች የተስፋይቱ ምድር (ፍሬና በረከት በሞላች ምድር) እየኖሩ በመና መኖር ግን አለመታደል ነው፡፡ ምክንያቱም በአካል ከምድረ በዳ ወጥቶ ነገር ግን የምድረ በዳን ሕይወት መቀጠል ስለሆነ፡፡ እግዚአብሄር ይህንን ጉስቁልና “ከዛሬ” በኃላ ከሕዝቡ ላይ ሲያስወግደውና ያንን በማድረጉ ደግሞ ደስ ብሎት ሲናገር እናያለን፡፡ “ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ “ ይላልና፡፡

Sermons

ንስሃ በፍሬ

Posted on
ሉቃ 13፡1-9 ንስሓ በፍሬ ECMYIS ,Evalgelical Church Mekane Yesus, Ethiopian Christian Church in Glasgow, Eritrean Christian Church in Scotland, Evangelical and Lutheran church,cross

በሕይወት ኖረን፣ ተጨማሪ የእግዚአብሄር ቃል፣ ተጨማሪ የእግዚአብሄር መልካምነት፣ የእግዚአብሄር ጥበቃ፣ መልካም ፍሬ ለማፍራት ይረዱን ዘንድ የተቀበልናቸው የጸጋ ሥጦታዎችና ተጨማሪ አገልግሎቶች ሁሉ በአሁንና በሚመጣው ዓመት መካከል ፍሬ አፍርተን እንድንገኝ ነው፡፡ እርሱ (ሠራተኛው) ግን መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ ዙሪያዋን እስክኰተኵትላትና ፋንድያ እስካፈስላት ድረስ በዚች ዓመት ደግሞ ተዋት። ወደ ፊትም ብታፈራ፥ ደኅና ነው፤ ያለዚያ ግን ትቈርጣታለህ አለው።” (ቁ 6-9)፡፡

ለእኛ “የሚቀጥለው ዓመት” የተባለው መቼ ይሆን? ከተሠጠን የጸጋና የእንክብካቤ ዘመን ምን ያክሉን እንዲሁ አሳልፈን ይሆን? ፍሬስ ይታይብን ይሆንን? በክርስቶስ በኩል ጽድቅን ከተቀበሉት አማኞችም ያንን የጽድቅ ፍሬ እያፈሩ እንድኖሩ ይፈልግባቸዋል፡፡ጌታ “እኔ የምወዳቸውን ሁሉ እገሥጻቸዋለሁ እቀጣቸውማለሁ፤ እንግዲህ ቅና ንስሐም ግባ።” ይላልና (ራዕ 3፡19)፡፡

Sermons

ኢየሱስ ሥራውን ቀጠለ

Posted on
I must work the works of him that sent me, while it is day: the night cometh, when no man can work. “ ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች ”Evangelical Church Mekane Yesus in Scotland, ECMYIS, Glasgow, Uk. Amharic service

ጌታ እየሱስ ብዙ የሚሠራቸው ሥራዎች ነበሩት፡፡ በተለይ ደግሞ አጋንንትን ማውጣት እና በሽተኞችን መፈወስ (ቁ.32)፡፡ ይህ ማለት የታሰሩንና ጤናቸውን ያጡትን የሰዎችን ልጆች ነጻ ማውጣት በቀረችው ጊዜ መፈጸም የሚፈልጋቸው ሥራዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን ይህንን ዓላማውን ትቶ እንዲሄድና ከሄሮድስ የመግደል ዕቅድ እንዲያመልጥ ስመክሩት እንመለከታለን፡፡“ከፈሪሳውያን አንዳንዱ ቀርበው፦ ሄሮድስ ሊገድልህ ይወዳልና ከዚህ ውጣና ሂድ አሉት።” (ቁ 31)
ኢየሱስ በዚህ ምድር ላይ የነበረውን ተልዕኮ (ሚሽን) ጨርሶ ከመሄዱ በፊት የተወሰነ ወይም ጥቂት ጊዜ እንደነበረው ያውቅ ነበረ፣ ይናገርም ነበረ፡፡ “ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሠራ የማይችልባት ሌሊት ትመጣለች” (ዮሓ 9፡4) ብሎአልና። ኢየሱስ ሰው ሊሠራበት የማይችልበት “ሌሊት” ይመጣል ሲል ሰው ሌሊቱ ሳይመጣ የተሠጠውን የቤት ሥራ በርትቶ መጨረስ እንዳለበት ለማሳሰብም ነው፡፡ …..

Sermons

የእምነት ቃል

Posted on
ወንጌላችን እንግዲህ ይህ ነው፡፡ በኢየሱስ አምኖ ስለመዳን፣ በትንሳኤው ጉልበት አምኖም ስለመጽደቅ፡፡ ዛሬ እኛም “ የምንሰብከው የእምነት ቃል ” ይህ ነው፡፡

… ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው፡: እንደ ሓዋሪያው አገላለጽ፣ በዘመኑ የነበሩት እስራኤላዊያን “የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም” (ቁ.3) ። ያ ማለት ምን ማለት ነው? ሰዎች ይጸድቁበትና ይድኑበት ዘንድ የተላከላቸውን ኢየሱስን ማመን ትተው፣ በሙሴ ህግ ላይ ሙጭጭ ብለው በመቆም፣ እጅግ እየደከሙ ግን ደግሞ ሳይጸድቁ ይኖራሉ፡፡
በዘመናችም ይህ በግልጽ ይታያል፡፡ ብዙ ሰዎች ኢየሱስን አምኖ በእርሱ ከመጽደቅ ይልቅ፣ “እኔ ክፉ ነገር አላደረግሁ፣ ሰው አልበድልም፣ አልሰርቅም፣ አላመነዝርም፣ እጾማለሁ፣ ለደሃ እሰጣለሁ፣ ወዘተ. እያሉ የራሳቸውን ጽድቅ ይደረድራሉ፡፡ መጽሓፍ ቅዱስ ግን እንዲህ ብሎ በግልጽ ያስቀምጣል

Sermons

እርሱን ስሙት

Posted on
እርሱን ስሙት::ኢየሱስን አለመስማት ለሰው ልጅ ሕይወት ትልቅ ጉዳት ነው፡፡ ስለዚህ ነው “እርሱን ስሙት፡፡” የሚል ድምጽ የመጣው፡ecmyis, Mekane Yesus in Scotland, Glasgow Mekane Yesus, Lutheran chuch in Glasgow, Evangelical Christian chuch in Scotland, Glasgow, Amharic Service, Afan Oromo, Tigrigna and Enlsih Bible daily verses. Sundy service

ኢየሱስን አለመስማት ለሰው ልጅ ሕይወት ትልቅ ጉዳት ነው፡፡ ስለዚህ ነው “እርሱን ስሙት፡፡” የሚል ድምጽ የመጣው፡፡
ከማናቸውም ጊዜ የበለጠ፣ በጸጋ ጊዜ ውስጥ አለን፡፡ በብዙ የእግዚአብሄር ምህረትና መልካምነት፣ በጸጋው በሚሠጡ የተለያዩ ለቤተክርስቲያን የተሰጡ ስጦታዎች ተከበን አለን፡፡ ጌታን ከፈለግነው ለማግኘት በካህናት ወይም በመላዕክት በኩል መቅረብ ወይም የበግ ጠቦት፣ ኮርማ ወዘተ.ማቅረብ አያስፈልገንም፡፡ ጌታ ኢየሱስ ራሱ የተከፈተ በር ሠጥቶናል፣ “ለምኑ ይሠጣችሁሃል፣ ፈልጉ ታገኛላችሁ፣ መዝጊያውን አንኳኩ ይከፈትላችሁሃል” ብሎ፡፡ “በስሜ የምትለምኑትን አብ ይሠጣችሃል” ብሎም መክሮአል፡፡ ግን ደግሞ በዚህ ሁሉ በረከትና ሥጦታ፣ በዚህ ትልቅ ዕድልና ጊዜ በአግባቡ እየተጠቀምን ይሆን?
ስንቶቻችን በዚህን ጊዜ እንኳ ኃጢአት ከብዶን እንኖራለን፣ ስንቶቻችን በዚህን ጊዜ ስንፍናና “እንቅልፍ” ከብዶን የምንናገረውንና የምናደርገውን እስከማናውቅ ድረስ እንቅልፍ ተጫጭኖናል?
እያዬን የማናይ፣ እየሰማን የማንሰማ፣ ጌታ ከእኛ ጋር እያለ የማናስተውል፣ ግን በእንቅልፍ ልብ የምንቀባጥር ጌታም የምታዝበን ስንቶች ነን?
ሕይወታችንና ዘላለማችን በኢየሱስ ውስጥ አለ፡፡ ኢየሱስን መስማት እግዚአብሄር አብ ከእኛ የሚፈለገው ትልቅ ነገር ነው፡፡ “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም።” ተብሎ ተጽፎአልና (ዮሃ 3፡26)፡፡ “እርሱን ስሙት፡፡”

Sermons

በጎ ማድረግ ተፈቅዶአል

Posted on
ኢየሱስም፦ እጠይቃችኋለሁ፤ በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳንን ወይስ መግደል? አላቸው። “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን፦ አንሄድባትም አሉ። እኔም፦ የመለከቱን ድምፅ አድምጡ ብዬ ጠባቆችን ሾምሁባችሁ፤ እነርሱ ግን፦ አናደምጥም አሉ። አሕዛብ ሆይ፥ ስለዚህ ስሙ፤ ማኅበር ሆይ፥ እነዚያ የሚያገኛቸውን እወቁ። ምድር ሆይ፥ ስሚ፤ እነሆ፥ ቃሌን ስላልሰሙ ሕጌንም ስለ ጣሉ በዚህ ሕዝብ ላይ የአሳባቸውን ፍሬ ክፉን ነገር አመጣባቸዋለሁ።”

ኢየሱስም፦ እጠይቃችኋለሁ፤ በሰንበት በጎ ማድረግ ተፈቅዶአልን ወይስ ክፉ? ነፍስ ማዳንን ወይስ መግደል? አላቸው። “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም፥ የቀደመችውንም መንገድ ጠይቁ፤ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደ ሆነች እወቁ፥ በእርስዋም ላይ ሂዱ፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ እነርሱ ግን፦ አንሄድባትም አሉ። እኔም፦ የመለከቱን ድምፅ አድምጡ ብዬ ጠባቆችን ሾምሁባችሁ፤ እነርሱ ግን፦ አናደምጥም አሉ። አሕዛብ ሆይ፥ ስለዚህ ስሙ፤ ማኅበር ሆይ፥ እነዚያ የሚያገኛቸውን እወቁ። ምድር ሆይ፥ ስሚ፤ እነሆ፥ ቃሌን ስላልሰሙ ሕጌንም ስለ ጣሉ በዚህ ሕዝብ ላይ የአሳባቸውን ፍሬ ክፉን ነገር አመጣባቸዋለሁ።”

Sermons

ስለነፍስ የሚሠጥ ቤዛ

Posted on
ስለ ነፍስ የሚሠጥ ቤዛ የለም፡፡ Mekane Yesus in Scotland,glasgow city, United kingodm. makaane Yesuus የወንጌል ሉቃ 6፡ 17-26

ከጊዜያዊ ሃብት፣ ጊዜያዊ ደስታ፣ ጊዜያዊ ሳቅ ና ጊዜያዊ አድናቆት ማግኘት ይልቅ ጊዜያዊ ችግራቸው፣ ጊዜያዊ ራባቸውና መገፋታቸው ዘላለማዊ ብጽዕናን ያስገኛልና፡፡ ኢየሱስን መከተል የራስን ነፍስ ማትረፍ ነው፡፡ ግን ከኢየሱስ ይልቅ ሌላውን ለማግኘት ከኢየሱስ መራቅ ነፍስን ማጉደል ነው፡፡ ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ እያለን ነው “ስለ ነፍስ የሚሠጥ ቤዛ የለም፡፡ የራስን ነፍስ ጥሎ ሌላ ሁሉ ትርፍ ማግኘት አስከፊ ክሳራ ነው፡፡”

Sermons

ታንኳህን ለጌታ

Posted on
መካነ የሱስ በስኮትላንድ፣ ስብከት፣ በሊሊ፣ አይዳ፣ ግላስጎ መካነ ኢየሱስ፣ ሉቃ 5 1-11፣ የእሁድ አገልግሎት፣ ታንኳሽን ጌታ ይፈልገዋል፡፡ ታንኳህን ለጌታ

በመጀመሪያ ታንኳን ብቻ የፈለገ ቢመስልም ለካስ ጌታ ጴጥሮስን ራሱን ፈልጎት ነበረ፡፡ እነርሱም ይህ ታላቅ ጥሪ በልባቸው ሚዛን ሲደፋ አሳ በማጥመድ ህይወት ውስጥ አይተውት የማያውቁ እጅግ ብዙ አሣ ይዘው ሳሉ ተሯሩጠው ገበያ ከማፈላለግ ይልቅ ጀልባቸውን ወደ ዳር አውጥተው ያ ሁሉ የተደነቁበትን ብዙ አሣ እዛው ጥለው ጌታን በህይወት ዘመን ሙሉ ለመከተል ወሰኑ፡፡ ከጌታ ካገኙት ብዙ አሣ ይልቅ ጌታን ራሱን መከተል የተሻለ ሆኖ አገኙት፡፡ ታንኳህን ለጌታ ሥጥ፡፡ እንቺም ታንኳሽን ለጌታ፡፡

Sermons

ከጸጋው ቃል የተነሣ

Posted on
ሁሉም ይመሰክሩለት ነበር ከአፉም ከሚወጣው ከጸጋው ቃል የተነሣ እየተደነቁ፦ ይህ የዮሴፍ ልጅ አይደለምን? ይሉ ነበር። ሉቃ 4፡22 “And all bare him witness, and wondered at the gracious words which proceeded out of his mouth. And they said, Is not this Joseph's son?” Luk 4:22 Glasgow city, Mekane Yesus congrigation, Scottish Ethiopians church, EECMY, ECMYIS, Mekane Yesus in Scotland, Mekane Yasus, Ethiopian Church in Glasgow, Scotland, Ethiopian Christina Community, Evangelical Church, Lutheran chuch in Glasgow, Scotland. we meet in St George's Tron Church, Church of Scotland, city center. Christian family, infant baptism is also practiced here. Eritrean Christian church from Lutheran chuch of Eritrea.

ኢየሱስ ያነበበው ክፍል እና የሚናገረው ነገር ወደ ማንነቱ ዕውቀት የሚመራ ቢሆንም፣ ሰዎች በእርሱ ማመን አልፈለጉም፡፡ በዓለማችን ውስጥ የሚፈጠሩት ሕብረተሰባዊ ቀውሶችም ሆነ መነቃቃቶች በአብዛኛቸው ቢጠኑ፣ ከተጽኖ አምጪ ንግግሮች ጋር ተያያዥነት እንዳላቸው እገምታለሁ፡፡ “የጠቢባን ቃል እንደ በሬ መውጊያ ነው” ፡፡ የበሬ መውጊያ የሚባለው፣ ደንባራውንና ደካማውን በሬ፣ ወደ ፊት ዘሎ እንዲሄድ የሚያደርገው ነው፣ ተኝቶም ከሆነ፣ ከተኛበት ቀስቅሶ የሚያስሮጥ ነገር ነው፡፡